በስዊድን መጠለያና ጥገኝነት ማግኘት

Skydd och asyl i Sverige – amhariska

ለርሶ ስዊድን አገር ጥገኝነት ለጠየቁ የሚያገልግል መረጃ፤ እዚህ ታች ቀርባዋል። በዚህ ጽሁፍ ላይ፤ የጥገኝነት ማመልከቻ ካስገቡና፤ ውሳኔ ከተሰጥዎት በኋላ ምን ሊያጋጥም እንደሚችል መረጃዎች ያነባሉ። እዚሁ ጽሁፍ ላይ በተጨማሪ፤ ጥገኝነት ጠያቂ እንደመሆንዎ መጠንም፤ ስለ ስራ፡ ስለ መኖርያ ቤት፡ ስለ ጤና-ጥበቃና ስለ ገንዘብ እርዳታም በተመለከተ፤ ስላልዎት መብትና ግዴታ ማንበብ ይችላሉ።

በአሁኑ ጊዜ


  • የቀን አበል እና የመኖሪያ ቤት ወጪን የሚመለከት ለውጥ

    የስደተኞች ጉዳይ ጽ/ ቤት የእርስዎን የቀን አበልና እና የመኖሪያ ቤት ድጎማ የማግኘት መብት በሚያጣራበት ወቅት ከአሁን በኋላ የባለቤትዎን ወይም የኑሮ ጓደኛዎን ገቢ ከግምት የሚያስገባና በዚያ ላይ ተመስርቶ ውሳኔ የሚሰጥ ይሆናል።

  • አሁን የጥገኝነት ጥያቄ ውሳኔ በፖስታ ይደርሶታል

    እስከ አሁን በነበረው አሰራር፣ የስደተኞች ጉዳይ ጽ/ ቤት የጥገኝነትን ውሳኔ የሚያሳውቀው፥ ባለ ጉዳዩን በጽ/ ቤቱ የመሰተንግዶ ክፍል ድረስ ጠርቶ በአካል በማነጋገር ነበር። ያ አሰራር አሁን ተለውጧል። ከማርች (mars) 1 ቀን ጀምሮ በስዊድን የጥገኝነት ጥያቄዎ ውሳኔ መኖሪያ አድራሻው ድረስ በፖስታ ይላክሎታል።